የምርጫ ባለድርሻ አካላት ጉባኤ ጥሪ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በተለያዩ ጊዜያት ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር የተለያዩ ውይይቶች በማድረግ ለቀጣዩ አገራዊ ምርጫ የሚያደርጋቸውን ዝግጅቶች ሲያሳውቅ እንደቆየ ይታወቃል፡፡ ቦርዱ በቅርቡ ካከናወናቸው ውይይቶች መካከል በጥቅምት ወር በአፍሪካ ህብረት በስብሰባ አዳራሽ ያከናወነው የምርጫ ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ የሁለት ቀን አለም አቀፍ ጉባኤ እንዲሁም የምርጫ ጊዜያዊ የጊዜ ሰሌዳን አስመልክቶ ከሚመለከለታቸው አካላት ጋር ያደረገው ምክክር ጥቂቶቹ ናቸው፡፡